Quantcast
Channel: Goolgule
Browsing all 562 articles
Browse latest View live

“የነጭ ወያኔዎች” ሥልጣን መልቀቅና የተቀሩት “የዳግም ውልደት”ክህደት

የህወሃትና የአሜሪካ ፍቅር ቀደም ሲል ይወራ እንደነበረው “በመካከላቸው ንፋስ ገባ” ከሚባልበት ደረጃ ባለፈ እየሰለለ መምጣቱን የሚጠቁሙ እውነታዎች እየታዩ ነው። ራሱ ህወሃት ይህንኑ ፍትጊያ የሚያጎሉ ጉዳዮች እያከናወነ ይገኛል። ለልዩነቱ መክረር ፍንጭ እየታየ ነው። ከኦባማ ዘመን ማብቃት ጋር ተያይዞ የቀድሞ ወዳጆቹ...

View Article


የጣና በለስ ታሪካዊ የልማት ፕሮጀክት፤ ከመፈራረስና ውድመት እስከ መሸጥ

የጣና በለስ ፕሮጀክት አጭር ታሪክ የጣና በለስ ፕሮጀክት ልማታዊ ግቦች/ህልሞች ምን ነበሩ? የጣና በለስ ፕሮጀክት በአፄው ስርዓት ተጠንስሶ፥ በደርግ አብቦ፥ በህወሀት/ኢህአዴግ እንዴትና ለምን ፈራረሰ? ዛሬ በጣና በለስ ላይ የተጋረጠው አዲስ እና አስደንጋጭ አደጋስ ምንድን ነው? መፍትሄውስ? መግቢያ የአባይ ተፋሰስ...

View Article


ጋምቤላ ልጆቿ በጥይት የተጨፈጨፉበት ምክንያት ይፋ ሆነ!

ዜናውን “መገጣጠም” ሲሉ በቁጭት ይገልጹታል። የትግራይ “ባለሃብቶች” በጋምቤላ መበደላቸውን ለውጭ አገርና ለአገር ውስጥ መገናኛዎች ያስታወቁበት ዕለትና የአኙዋክ ምስኪኖች በምድራቸው በግፍ የተጨፈጨፉበት ቀን ተሳሳመ። ደም እንደጎርፈ በፈሰሰበት፣ ንጹሃን እንደ እንስሳ የተቀሉብት ቀን ተዘንግቶ በሙታን ዱካ ተተክተው...

View Article

በጋምቤላ የከሸፈው “ኢንቨስትመንት”

በጋምቤላ የአኙዋክ ተወላጆች ተጨፍጭፈውና ከመሬታቸው ተፈናቅለው “ለሰፋፊ እርሻ” በሚል ሲቸበቸብ ከነበረው መሬት “ወደ ሥራ የገባው” 15በመቶው ብቻ መሆኑን ህወሃት/ኢህአዴግ አስታወቀ፡፡ ለ“እርሻ ልማት” በሚል 5ቢሊዮን ብር ብድር ተሰጥቷል፡፡ የመሬት ካርታ “ከቢሮ ውጪ በመኖሪያ ቤቶችና በጫት ቤት ውስጥ” ሲሰራ...

View Article

ኢህአዴግ በአሜሪካ የጉዞ ማዕቀብ ክፉኛ ተሽመድምዷል

አሜሪካ ባልተለመደ ሁኔታ ኢህአዴግን ከመውቀስ አልፋ እያስጠነቀቀች ነው። ኢህአዴግ በበኩሉ የጉዞ ማዕቀቡ እንዲነሳለት እየወተወተ ስለመሆኑ በተለያዩ መገናኛዎች ተደምጧል። የጎልጉል መረጃ አቀባይ የዲፕሎማሲ ምንጮች እንዳሉት አሜሪካ ለኢህአዴግ ጥያቄ መልሷ “ለጊዜው ጥሪ አይቀበልም” የሚል ሆኗል። እነዚሁ ክፍሎች...

View Article


የህወሃት ራስህን አድን “ጥልቅ ተሃድሶ” ሦስት ኦህዴድን ፈጠረ

ህወሃት በተለያዩ ጊዚያት አደጋ ሲገጥመው የሚዘይደው የማምለጫ ስልት በአካባቢው ባሉ “አጋሮቹ” ዘንድ “ዘመቻ ራስህን አድን” የሚል ስያሜ አለው። ይኸው ዘመቻ በኦሮሚያ ኦህዴድን እንዳራባው ነው የሚነገረው። የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት ኦህዴድ ውስጥ ያለው ፖለቲካዊ ችግር ተዳፈነ እንጂ አልበረደም። ይልቁኑም...

View Article

የማናውቀው ታሪካችን

ታሪካችንን ባለማወቃችን ሁሌም ወደኋላ በመገስገስ ላይ እንገኛለን፤ ሰሞኑን አንዳንድ ዜና መዋዕሎችን ማንበብ ጀምሬ እስካሁን አራት ያህል አንብቤአለሁ፤ ከዚህ በፊት እየተንገዳገድሁ በግዕዝ አንብቤአቸዋለሁ፤ ዛሬ የሲራክ አሳታሚ ድርጅት በአማርኛ እያሳተማቸው በመሆኑ ምስጋና ይድረሰውና ሳልንገዳገድ በአማርኛ እያነበብሁ...

View Article

በሚገዛው ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀ አገዛዝ –ተግባሩን “ስኬት” ሲል ገመገመ

ግድያ፣ አፈና፣ ቶርቸር፣ ረሃብ፣ የጅምላ ጭፋጨፋ – ስኬት በቅርቡ ሃይለማርያም ደሳለኝ እንደ እርሱ “አሽከር” ለሚባለው የኢህአዴግ ሸንጎ ንግግር ሲያደርግ ኢህአዴግ የወሰዳቸውና እየወሰደ ያለው እጅግ አረመኔነት የተሞላበት አሠራር የሚደነቀ መሆኑን አስታውቋል። “መቶ በመቶ መርጦኛል፤ እመራዋለሁ” በሚለው ህዝብ ላይ...

View Article


ፖለቲከኞችን አስሮ ድርድር፤ ካድሬ አሰልፎ እርቅ –“አዙረኝ አታዙረኝ” እንዳይሆን

ከውጭ ያለው ችግር ከተፋዘዘ ብሄራዊ ስሜት ጋር!! ኢህአዴግ በከፋ ቀውስ ውስጥ ይገኛል። ቀውሱ ከውስጥ ብቻ ሳይሆን ከውጭም ነው። ሰሞኑን ይፋ የሆኑ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ውጥረቱ በውስጥ ካለው ብሄራዊ አንድነትና ኅብረት መደብዘዝ፣ ህዝብ እያደር ስርዓቱን መጠየፉ፣ የራሱ የፓርቲው መበስበስና በሙስና መርከስ፣ የውስጥ...

View Article


ቀዝቃዛዉ ጥምቀትና የበረከት ስምዖን “ግብረኃይል”በጎንደር

ጥምቀትን ያለ ጎንደር ማሰብ የሚቻል አይደለም። ጥምቀት ከኃይማኖታዊ በዓልነቱ ባሻገር ባህላዊ ገጽታ የሚንጸባረቅበት ጉምቱ የአደባባይ በዓል ነበር። የጎንደር ጥምቀት እንኳን ለቱሪስቶች ለቀየዉ ነዋሪዎችም ታይቶ የሚጠገብ አልነበረም። በየዓመቱ በአማካይ 1500 የሚደርሱ ቱሪስቶች ከተለያዮ የአለማችን ክፍሎች ተሰባስበዉ...

View Article

ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም

አንደኛ፣ ገና በልጅነቴ አሥር ዓመት ግድም ሲሆነኝ አንድ በድቀድቂት ከእንጦጦ ወደታች የሚወርድ ኢጣልያዊና እኔ ተጋጠምን፤ እሱ በዚያ በጥቁር ድንጋይ ኮረት በረበረበበት መንገድ ላይ ሲጓዝ ወደ እንጦጦ የሚወጣ ወታደሮችን የጫነ ከባድ መኪና ቆሞ ነበር፤ በዚያ መኪና ላይ አንድ ዝንጀሮ ነበር፤ የኔ አትኩሮት በዚህ ዝንጀሮ...

View Article

መስጊዳቸው ለተቃጠለባቸው የአይሁድ ቤተመቅደስ ቁልፍ ተሰጣቸው

በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በቪክቶሪያ ከተማ መሰጊዳቸው ለተቃጠለባቸው ሙስሊሞች በከተማዋ የሚገኘው የአይሁድ ምኩራብ በሩን ከፈተላቸው፡፡ እንደ ሲኤንኤን ዘገባ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በቪክቶሪ ቴክሳስ የሚገኘው እስላማዊ ማዕከል (መስጊድ) ቃጠሎ ደርሶበት ነበር፡፡ ይህንን የተመለከቱ በከተማው...

View Article

የድርድር ቅድመ ጸብ “በተቃዋሚዎች”መካከል እና የጠብ-መንጃ “ሰላም”እስከመቼ?

ቅድሚያ “የታሰሩ ይፈቱና አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ” የሚለው ኢህአዴግን ሳይሆን “ተቃዋሚዎችን” አላስማምም፤ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች “ቅድሚያ ይፈቱ” የማያስማማቸው ተቃዋሚዎችን አንድ የማድረግ ሃሳብም አለ። ይህንን ሃሳብ የሚያራምደው ደግሞ ኢዴፓ ነው። የህብረቱን ጥያቄ በፕሮግራም ደረጃ አርቅቆ...

View Article


የኢህአዴግ ከፍተኛ ሹሞችን ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅም የሚያስከብር አዋጅ ጸደቀ

ከሁለት ዓመት በፊት በጭምጭምታ ደረጃ ወሬዉ ወደ አደባባይ የወጣዉ ባለሥልጣናት “ጡረታ” ሲወጡ የሚከበርላቸዉ ጥቅማጥቅም አሁን “ህጋዊ  ዕዉቅና” አግኝቷል። ሐሙስ ዕለት በዋለዉ የኢህአዴግ “ፓርላማ” የህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከኃለፊነታቸዉ ሲነሱ ጥቅማጥቅማቸዉን የሚያስከብር አዋጅ...

View Article

በጎንደር ከተማ በተቀሰቀሰው ህዝባዊ አመጽ ንብረታቸዉ ወድሟል የተባሉ የትግራይ ሰዎች ካሳ ሊከፈላቸዉ ነዉ

በ2008ዓ.ም. መገባደጃ ወራት ላይ የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አስተባባሪ የኮሚቴ አባላትን የህወሃት/ኢህአዴግ ኃይሎች በጎንደር ከተማ ለማፈን ያደረጉት ሙከራ ከፍተኛ ህዝባዊ ቁጣ ቀስቅሶ የህይወትና የንብረት ዉድመት መድረሱ ይታወሳል። በወቅቱ “ንብረታቸው ወድሟል” የተባለላቸው የትግራይ ተወላጆች የካሣ ክፍ...

View Article


የጦር መሳሪያ ዋጋ አሻቀበ፤ ክላሽንኮቭ እስከ 60 ሺህ ብር ይሸጣል፣ መሳሪያ ቁልፍ ሃብት ሆኗል!

ሱዳንና ህወሃት የመሳሪያ ዝውውርን ለመግታት ተስማሙ ትግራይ ክልል ኢትዮጵያን ወክሎ ከሱዳን ጋር ስምምነት አደረገ ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የተቀሰቀሰዉ አመጽ ማህበራዊ መሰረቱን እያሰፋ በጎንደርና በጎጃም የተለያዩ ዞኖችን፣ ወረዳዎችን፣ የከተማ አስተዳደሮችና የገጠር ከተሞችን ያዳረሰ ህዝባዊ...

View Article

ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ

የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት የለም” እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ። እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች...

View Article


ብአዴን አከርካሪው ላይ ተቆርጧል –ሕዝብ እነ ደመቀን “በቃችሁ” አላቸው!

በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ወደ ጎንደር አቅንተዉ ነበር፡፡ በደመቀ መኮንንና በገዱ አንዳርጋቸዉ የተመራዉ ከፍተኛ አመራር ቡድን ሦስት ዋናዋና ቁልፍ ተልዕዎኮችን ለማሳካት ከባህርዳር እንደተንቀሳቀሰ የጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ የብአዴን ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡ አንደኛ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የመራዘሙን...

View Article

የአለቃ ጸጋየ በርሄና የህላዊ ዮሴፍ ወጎች፤ ከሹመት እስከ ሽረት፤

የህወሓት-እስራኤል ቀጣይ የፖለቲካ ቁማር! አሁን ባለዉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፍ ለህወሓት/ኢህአዴግ ቁልፍ የስጋት ምንጩ የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ጎራ ነዉ፡፡ የድህረ-ምርጫ 97 ዉርስ ዕዳ የሆነዉ የዲያስፖራዉ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እንደ ሀገር ቤቱ ሁሉ በዘዉግ ፖለቲካ የሚታመስ ቢሆንም በጋራ ጠላት...

View Article

ታጋይ ጎቤ መልኬ በአዴት ጦርነት ተሰዋ፤ “የህወሃት ወራሪ ሃይል ጉዳት ደርሶበታል”

“ጎቤ ሲሰዋ አዳዲስ ጎቤዎች ትግሉን ተቀላቅለዋል’’ “አርበኛ ጎቤ መልኬ ተሰዋ” ሲሉ በአካባቢው የሚገኙ የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ገለጹ። ህወሃት የሚመራው ሰራዊት ክፉኛ ጉዳት ደርሶበታል። ዜናው ኢህአዴግ በሚያስተዳድራቸውም ሆነ በሚደጉማቸው መገናኛዎች ይፋ አልሆነም። ለነጻነት ሃይሎች ጋር ግንኙነት አላቸው የሚባሉ...

View Article
Browsing all 562 articles
Browse latest View live